· ኦፊሴላዊ ስም፡ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት
· ርእሰ ከተማ፡ አዲስ አበባ
· የመልክአ ምድር አቀማመጥ፡ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ በልዩ አጠራሩ “የአፍሪካ ቀንድ” በሚባለው የአፍሪካ ክፍል ትገኛለች፡፡ በምስራቅ ከጅቡቲ እና ሶማሊያ፣ በሰሜን ከኤርትራ፣ በምዕራብ ከሱዳን እንዲሁም በደቡብ ከኬንያ ጋር ትዋሰናለች፡፡
· መገኛ ቦታ፡ ኢትዮጵያ ከምድር ወገብ ከ 3o እስከ 15o በሰሜን፣ እና 33o – 48o በምስራቅ ከግሪንዊች ሜሪድያን ትገኛለች፡፡
· የቆዳ ስፋት:
· አጠቃላይ የቆዳ ስፋት፡ 1.14 ሚሊዮን ስኩዌር ኪ.ሜትር
· ሊታረስ የሚችለው መሬት፡ 45%
· በመስኖ ሊለማ የሚችል: 10 ሚሊዮን ሄክታር
· በመስኖ የለማ: ወደ 3%
· ስነ-ህዝብ
· ጠቅላላ የህዝብ ቁጥር: ወደ 80 ሚሊዮን
o የሴቶች ቁጥር፡ 39.9 ሚሊዮን
o የወንዶች ቁጥር:40.1 ሚሊዮን
በገጠር የሚኖር: 66.8 ሚሊዮን
በከተማ የሚኖር:13.2 ሚሊዮን
የህዝብ ቁጥር ዕድገት በአመት: 2.73%
የህዝብ ጥግግት:66.5:1 ስኩ.ኪ.ሜ
· አማካኝ የአንድ ሰው የእድሜ ጣሪያ
o ወንድ: 53.42 ዓመት
o ሴት:55.42 ዓመት
· የዕድሜ ስብጥር (በመቶኛ)
o 0-14: 42.8%
o 15-19: 10.5%
o 20-49: 37.4%
o 50-59: 4.9%
o 60 and above: 4.4%
· የስራ ዕድሜ ክልል (በመቶኛ)
o በከተማ: 54.7%
o በገጠር: 50.6%
· ቋንቋ: አራት ዋና ዋና የቋንቋ ቤተሰቦች ሲገኙ በአንድነት ወደ 80 ቋንቋዎች በሀገሪቱ ይነገራሉ
§ የስራ ቋንቋ፡ አማርኛ
§ የእንግሊዝኛ ቋንቋም ለቢዝነስ እንቅስቃሴዊች ለባንክ፣ ለኢንሹራንስ መስሪያ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ማስተማሪያም በመሆን ያገለግላል፡፡
· ዋነኛ ሀይማኖቶች፡ ክርስትና እና እስልምና
· የመንግስት አወቃቀር፡ ፌዴራላዊ ሲሆን በ9 ክልላዊ መንግሰታት እና በሁለት የከተማ መስተዳደር የተዋቀረ ነው፡፡
· ብሄራዊ የህግ አውጭ አካል፡ ፓርላማ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ናቸው፡፡
· ምርጫ፡ በየአምስት አመቱ
· ከፍታ፡ ኢትዮጵያ ከ148 ሜትር ከባህር ጠለል በታች ከሚገኘው የዳሎል ዝቅተኛ ቦታ እስከ 4620 ሜትር የባህር ጠለል በላይ ከፍታ እሰካለው የራስ ዳሸን ተራራ የሚደርስ የከፍታ ልዩነት አላት፡፡
· የአየር ንብረት፡ የሙቀት መጠኑ ከ20 oC እስከ 30 oC ይደርሳል፡፡ የዝናብ መጠኑ ከ200ሚ.ሜ እስከ 2000ሚሜ በአመት ይደርሳል፡፡
· የሰዓት አቆጣጠር፡ ጂኤምቲ +3
· ዝናባማ ወቅቶች፡ ኢትዮጵያ ከፍተኛ የዝናብ መጠን የሚኖራት በሰኔ፣ ሀምሌና ነሀሴ ሲሆን በየካቲትና መጋቢት አነስተኛ የዝናብ መጠን ይኖራታል፡፡
· የመገበያያ ገንዘብ:
· ትንሹ የገንዘብ መለኪያስ: ብር
· 1 ብር= 100 ሳንቲሞች
· የብር ኖቶች፡ ባለ 1፣ 5፣ 10፣ 50፣ እና 100 ብር
· የመዳብ ሳንቲሞች፡ 1፣5፣10፣25፣ እና 50 ሳንቲሞች
· የውጭ ምንዛሬ አገልግሎት በአየር መንገዶች እና ፈቃድ ባለቸው ሆቴሎች ይገኛል፡፡