Embelem of Federal Democratic Republic of Ethiopia Official Portal of Federal  Democratic Republic of Ethiopia  
Home Home Citizens Citizens Government Government Businesses Businesses Forigners Forigners NGOs NGOs Decrease font Increase font
 

 የክልል መንግስታት

ኢትዮጵያ 1.1 ሚሊዮን ስኩዌር ኪ.ሜ የሚሆን  የቆዳ ስፋት ያላት ሀገር ስትሆን በአሁኑ ወቅትም ወደ 79 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ አላት፡፡ ከዚህም ውስጥ ወደ 84 ከመቶ የሚጠጋው በገጠሪቱ የኢትዮጵያ ክፍል ሲኖር የተቀረው በከተማና ከፊል ከተማ በሆኑ ቦታዎች ይኖራል፡፡ ኢትዮጵያ የፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት አወቃቀር ሲኖራት በ9 የብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት እንዲሁም በሁለት የከተማ መስተዳድሮች የተዋቀረች ነች፡፡ አወቃቀራቸውም በሕገ መንግስቱ በተደነገገው መሰረት «በህዝብ አሰፋፈር፤ ቋንቋ፤ ማንነት እና ፈቃድ ላይ» ተመስርቶ ሲሆን ክልሎቹም :- የትግራይ፣ የአፋር፣ የአማራ፣ የኦሮሚያ፣ የሶማሌ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች፣ የጋምቤላ እና የሀረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት ሲሆኑ በተጨማሪም የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ መስተዳደሮች ይገኙበታል፡፡

እነዚህ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስታት አንዲሁም ሁለቱ የከተማ መስተዳደሮች በ800 ወረዳዎቸና ወደ 15000 በሚጠጉ ቀበሌዎች(5000 የከተማና 10000 የገጠር) የተከፋፈሉ ናቸው፡፡

Map of Regional States 


 

©የቅጂ መብት 2003 የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት
የግላዊ ጉዳይ ጥበቃ ፖሊሲ |  የአጠቃቀም ደንቦች |  ኃላፊነትን ስለመወሰን | 
ተደራሽነት |  የደንበኞች ቻርተር