አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስልጉ መስፈርቶች
- በህግ አግባብ የተዘጋጀ የውል ፅሁፍ /ፎርም/
- ውሉ የተለየ ንብረትን ወይም መብትን የሚመለከት ከሆነ ባለቤትነትን የሚያረጋግጥ ማስረጃ
- እንደአስፈላጊነቱ እና እንደ ንብረቱ ዓይነት ክሊራንስና ሌሎች የድጋፍ ማስረጃዎች
አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከናወኑ ሂደቶች
- ባለጉዳዩ ሰነዱ ተረጋግጦ እንዲመዘገብለት ጥያቄ ያቀርባል
- ስምሪትና መስተንግዶ ሠራተኛ አማጣጥኖ ያሠማራል
- የስራ ክፍሉ ኃላፊ ለህግና ለሞራል የማይቃረን መሆኑን ይመረምራል
- አጣሪና አፈራራሚ ሠራተኛ ያጣራል፣ ያፈራርማል፣ ይመዘገባል
- ገንዘብ ተቀባይ የአገልግሎትና የቴምብር ቀረጥ ክፍያ ያሰባስባል
- ሠነድ አረጋጋጭና መዝጋቢ ሠራተኛ ሰነዶችን በማያያዝና ማህተም በማድረግ ቁጥርና ቀን ይሰጣል
- የስራ ክፍሉ ኃላፊ በመፈራረም ቲተሩን ያስቀምጣል
- የማህተምና ዕደላ ሠራተኛ በየገፁ ላይ ማህተም በማድረግ የባለ ጉዳዩን ድርሻ ይሠጣል የሥራ ሂደቱን ቀሪ ሰነድ ያስተላልፋል