አገልግሎቱን ለማግኘት መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
- እንዲረጋገጥለት የሚፈልገውን ሠነድ ዋናውንና ፎቶ ኮፒ
- ማንነቱን የሚገልፅ የቀበሌ መታወቂያ
አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከናወኑ ሂደቶች
- የሰነዶች ማረጋገጫ ክፍል በመሄድ ማቅረብ የሚገባቸውን ሠነድ ያቀርባል
- ትክክለኝነቱ ይረጋገጣል
- ወደ ሒሳብ ክፍል በመሄድ የአገልግሎት ማስፈፀሚያ ሠነድ ይዘጋጅለታል
- በሠነዱ ላይ የተገለፀውን የገንዘብ መጠን በዛው ክፍል ይከፍላል
- የሠነዶች ማረጋገጫ ክፍል በመሄድ የከፈለበትን ደረሠኝ ያቀርባል
- መክፈሉ ይረጋገጣል
- በመጨረሻም እንዲረጋገጥ የሠጠው ሰነድ ላይ ትክክለኛ መሆኑን ለማረጋገጥ በዛው ክፍል ማህተም ይደረግበታል