አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች
o በራሱ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ ግምቱ ከ15.000 ብር የማያንስ ተንቀሳቃሽ ወይም ቋሚ ንብረት ሲያቀርብ
o የኮርፖሬሽኑ ደንበኛ የሆነ ግለሰብ በዋስትና ሰጪነት ሲቀርብና ዋሱም እዳ ሲኖር ለመክፈል ፈቃደኛ መሆኑን በጽሁፍ ሲያረጋግጥ
o እውቅና ካለው ትልቅ የግል ድርጅት ወይም የመንግስት መ/ቤት ውስጥ በሚሠራ ሠራተኛ ዋስትና ሰጪነት
o ግምቱ ከ15.000 ብር የማያንስ ቋሚ ወይም ተንቀሳቃሽ ንብረት ያለው ግለሰብ ዋስትና ሰጪ ከማንኛውም መታወቂያ ጋር ሲቀርብ መስተናገድ ይቻላል
አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከናወኑ ሂደቶች
- የሽያጭ ማዕከል ቢሮ በመሄድ ማመልከቻ ያቀርባል
- የሽያጭ ማዕከል ቢሮ ማመልከቻውን ይመለከታል
- የሽያጭ ማዕከል ቢሮ ማመልከቻውን ከመረመረ በኃላ ወደ ኢንስታሌሽን ክፍል ይላካል
- ኢንስታሌሽን ክፍል በደንበኛው አካባቢ ክፍት መስመር እንዳለ ይመለከታል
- የሽያጭ ማዕከል ቢሮ በመሄድ የአገልግሎት ክፍያ ይከፍላል
- የከፈለበትን ደረሰኝ ኢንስታሌሽን ክፍል ያቀርባል
- በዛው ቢሮ ቀነ ቀጠሮ ይሠጠዋል
- የፊክስድ ላየን ስልክ ቀፎ በመግዛት ቤቱ ይጠብቃል
- መስመሩ ከተገኘ በኋላ ቤቱ በመሄድ መስመር ይዘረጋል