Embelem of Federal Democratic Republic of Ethiopia Official Portal of Federal  Democratic Republic of Ethiopia  
Home Home Citizens Citizens Government Government Businesses Businesses Forigners Forigners NGOs NGOs Decrease font Increase font
 

 የጠቅላላ ውክልና ሥልጣን መስጠት

    አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች 

  •  በሕግ አግባብ የተዘጋጀ የውክልና ስልጣን መስጫ ሠነድ
  • በውክልና ማስረጃው ላይ የተጠቀሰ የተለየ ንብረት ወይም መብት ካለ የወካይ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ

 አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከናወኑ ሂደቶች

  1. ባለ ጉዳዩ ሠነዱ ተረጋግጦ እንዲመዘገብለት ጥያቄ ያቀርባል

  2. ስምሪትና መስተንግዶ ሠራተኛ አመጣጥኖ ያሠማራል

  3. የስራ ክፍሉ ኃላፊ ለሕግና ለሞራል የማይቃረን መሆኑን ይመረምራል 

  4. አጣሪና አፈራራሚ ሠራተኛ ያጣራል፣ያፈራርማል፣ይመዘግባል

  5. ገንዘብ ተቀባይ የአገልግሎትና የቴምብር ቀረጥ ክፍያ ይሰበስባል

  6. ሠነድ አረጋጋጭና መዝጋቢ ሠራተኛ ሰነዶችን በማያያዝና ማህተም በማድረግ ቁጥርና ቀን ይሰጣል

  7. የስራ ክፍሉ ኃላፊ በመፈረም ቲተሩን ያስቀምጣል 

  8. የማህተምና የዕደላ ሠራተኛ በየገፁ ላይ ማህተም በማድረግ የባለ ጉዳዩን ድርሻ ይሠጣል የሥራ ሂደቱን ቀሪ ሰነድም ያስተላልፋል

©የቅጂ መብት 2003 የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት
የግላዊ ጉዳይ ጥበቃ ፖሊሲ |  የአጠቃቀም ደንቦች |  ኃላፊነትን ስለመወሰን | 
ተደራሽነት |  የደንበኞች ቻርተር