የመንጃ ፈቃድ አይነቶች
1. ሞተር ሳይክል
2. አውቶ ሞቢል
3. ታክሲ 1
4. ታክሲ 2
5. የህዝብ 1
6. የህዝብ 2
7. ደረቅ ጭነት 1
8. ደረቅ ጭነት 2
9. ደረቅ ጭነት 3
10. ፍሳሽ 1
11. ፍሳሽ 2
|
አገልግሎት ላይ ያሉ የመ.ፈ.አይነቶች |
የጽሁፍ ስልጠና ሰዓት |
የተግባር /የመኪና/ስልጠና |
የአገልግሎቶቹ ክፍያ |
የትምህርት ደረጃ |
ዕድሜ |
|
አውቶ ሞቢል |
54.50 |
30 ሰዓት |
2365 |
4ኛ ክፍልና በላይ |
18 ዓመትና በላይ |
|
ደረቅ ጭነት 1 |
60.50 |
35 ሰዓት |
3075 |
8ኛ ክፍልና በላይ |
21 ዓመትና በላይ |
|
ደረቅ ጭነት 2 |
60.50 |
50 ሰዓት |
5375 |
8ኛ ክፍልና በላይ |
24 ዓመትና በላይ |
|
ደረቅ ጭነት 3 |
60.50 |
65 ሰዓት |
8428 |
8ኛ ክፍልና በላይ |
24 ዓመትና በላይ |
|
ታክሲ 2 |
79.50 |
30 ሰዓት |
2735 |
8ኛ ክፍልና በላይ |
25 ዓመትና በላይ |
|
የህዝብ 1 |
79.50 |
45 ሰዓት |
3935 |
8ኛ ክፍልና በላይ |
24 ዓመትና በላይ |
አገልግሎትን ለማግኘት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች
· የቀበሌ ነዋሪነት ማረጋገጫ መታወቂያ
· 4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ
· የትምህርት ማስረጃ
አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከናወኑ ሂደቶች
1. በመንገድ ትራንስፖርት እውቅና በተሠጣቸው የመንጃ ፈቃድ ስልጠና የሚሠጡ ትምህርት ቤቶች በመሄድ መመዝገብ
2. በትምህርት ቤቱ ሲመዘገቡ የሜዲካል ምርመራ ከጤና ጣቢያ እንዲያመጡ ደብዳቤ ይሠጣቸዋል
3. የተሠጣቸውን ደብዳቤ በመያዝ ጤና ጣቢያ የሜዲካል ምርመራ ማከናወን
4. የተመረመሩበትን ውጤት በተመዘገቡበት ት/ቤት በቀጠሮ ቀን ማቅረብ ማውጣት
5. በሚፈልጉት የመንጃ ፈቃድ አይነት በተሠጣቸው ሰዓት መሠረት የጽሁፍ /የንድፈ ሀሳብ/ ስልጠና ማከናወን
6. የጽሁፍ /የንድፈ ሀሳብ/ ስልጠናውን ከጨረሱ በኋላ የተግባር /የመኪና/ ትምህርት እንዲወስዱ ቃሊቲ በትምህርት ቤቱ መኪና እንደ ሰዓቱ በቀን ለአንድ ሰዓት ስልጠና ይሠጣል
7. የተግባር ስልጠናው ካለቀ በኋላ ቃሊቲ በሚገኘው መንገድ ትራንስፖርት የፈተና ማስቀጠሪያ ደብዳቤ ይሠጣቸዋል
8. የተሠጣቸውን ደብዳቤ ለቃሊቲ መንገድ ትራንስፖርት የፈተና መስጪያ ቢሮ ያቀርባሉ
9. በደብዳቤው መሠረት የፈተና ቀን ቀጠሮ ይሠጣቸዋል
10. በቀጠሮ ቀን በመሄድ የቃል /የጽሁፍ/ እና የተግባር /የመኪና/ ጠዋትና ከሠአት ፈተና ይፈተናሉ
11. የፈተናውን ውጤት በዛው እለት እንዲያውቁ ይደረጋል
12. በፈተና መስጪያ ቢሮ 2 ጉርድ ፎቶ ግራፍ ያቀርባሉ
13. በዛው ቢሮ የ5 ብር ቴምብር ገዝተው ያቀርባሉ
14. የአገልግሎትና የመንጃ ፈቃድ ደብተር ክፍያ በገንዘብ ቤት ይከፍላሉ
15. የተከፈለበትን ደረሠኝ በፈተና መስጪያ ቢሮ ያስገባሉ
16. በክፍለ ከተማቸው በሚገኝ የመንገድ ትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መንጃ ፈቃዱን እንዲወስዱ ቀጠሮ ይሠጣቸዋል
17. በቀጠሮ ቀን በክፍለ ከተማው ትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመሄድ መንጃ ፈቃዱን ይወስዳሉ