አገልግሎቱን ለማግኘት መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
- ማንነቱን የሚገልፅ የቀበሌ መታወቂያ
- በተወካይ ከሆነ ሕጋዊ የውክልና ወረቀት
አገልግሎቱን ለመግኘት የሚከናወኑ ሂደቶች
- በመጀመሪያ ሬጅስትራር ቢሮ በመቅረብ ክሱ አግባብነት እንዳለው ያረጋግጣል
- ወደ ፋይል ከፋች ይመራል
- የአገልግሎቱ ማስፈፀሚያ ክፍያ ሰነድ በእዛው ክፍል ይረጋገጣል
- የዳኝነቱን ሂሣብ ከከፈለ በኋላ ወደ ሬጅስትራር ቢሮ በመሄድ የከፈለበት ደረሰኝ ይረጋገጣል
- ችሎት ቀጠሮ ይያዝለታል
- ውሣኔ በተሰጠ በ3ቀናት ውስጥ የውሣኔውን ግልባጭ መውሰድ ይቻላል