አገልግሎቱን ለማግኘት መሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች
- ከአንድ አመት በላይ የሆነ ህጋዊ ፓስፖርት
- ፓስፖርት ኮፒ እና የፓስፖርት የቪዛ ገፅ
- ከሚሠራበት ድርጅት የድጋፍ ደብዳቤ
- ህጋዊ የስራ ፈቃድ
- ከሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የድጋፍ ደብዳቤ
አገልግሎቱን ለማግኘት የሚካሄዱ ሂደቶች
- የውጭ ዜጎች መስተናገጃ ክፍል በመሄድ መቅረብ የሚገባቸውን ሠነዶች ያቀርባል
- ትክክለኛነቱ ይረጋገጣል
- ሒሳብ ክፍል በመሄድ የአገልግሎት ማስፈፀሚያ ሠነድ ይዘጋጅለታል
- በሠነዱ ላይ የተገለፀውን የሒሳብ መጠን በዕዛው ክፍል ይከፍላል
- በውጭ ዜጎች መስተናገጃ ክፍል በመሄድ የከፈለበትን ደረሠኝ ያቀርባል
- መክፈሉ ይረጋገጣል
- በመጨረሻም በዕዛው ክፍል የመኖሪያ ፈቃድ ይሠጠዋል