አገልግሎቱን ለማግኘት የሚያስፈልጉ መስፈርቶች
- ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ፎቶ ኮፒ
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ምስክር ወረቀት ፎቶ ኮፒ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ለመመዝገብ ከ500 ሺህ ብር በላይ አመታዊ ገቢ ያለው መሆን አለበት
- ከላይ የተጠቀሱትን ለማመሳከር ዋናውን ማቅረብ አለባቸው
አገልግሎቱን ለማግኘት የሚከናወኑ ሂደቶች
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የማመልከቻ ፎርም በገቢ አሠባሰብና አወሳሰን ክትትል ወሳኝ ስራ ሂደት ቢሮ በመውሰድ ይሞላል
- የተሞላው ፎርም በዛው ቢሮ ይቀርባል
- በፎርሙ መሰረት በማህደር መዝገብ ላይ ይመዘገባል
- የማህደር ቁጥር ይሠጠዋል
- በዛው ቢሮ በማህደር ቁጥሩ መሠረት የተጨማሪ እሴት ታክስ የመመዝገብ አገልግሎት ይከናወናል